ጎንደር ከተማ እስራኤል ከሚገኙ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሂዷል፡፡የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ከእስራኤል ም/አምባሳደር ቶመር ባርላቪ ጋር በቱሪዝምና የእህትማማች ከተሞችን ማጠናከር በሚቻልብት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡ከዚህ ባለፈም የልማት እንቅስቃሴዎችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የጎንደር ከተማ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡ምክክሩ ጎንደር ከተማ እስራኤል ካሉ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።