ለአረጋውያን እና በኢኮኖሚ ዝቅተኛ ለሆኑ ወገኖች የሚደረገው የቤት ሥራ እና የአዋሬ አካባቢ የለውጥ እንቅስቃሴ ላለፉት ስድስት ዓመታት በተግባር ላይ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።የዘንድሮው የግንባታ ሂደት ፍጥነት እና ጥራት ላጣመረ የሥራ ባሕል ምሳሌ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል። የቤት ግንባታ ብቻ ሳይሆን የአረንጓዴ ሥፍራዎቹ ግንባታ የጋራ እሳቤን እና ጉርብትናን የሚያዳብሩ፣ ለሰው ልጅ የሚገባውን የከበረ የአኗኗር ዘይቤ የሚያዳብሩ ናቸው ብለዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።