ይህ እርምጃ የተወሰደው የቱርክ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን የሀኒየህን ግድያ አስመልክቶ የወጡ የሀዘን መግለጫዎች ኢንስታግራም አጥፍቷል ሲሉ ትችት ከሰነዘሩ በኋላ ነው
ቱርክ ኢንስታግራም በግዛቷ እንዳይሰራ እግድ ጣለች።
ቱርክ የሜታው የማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያ ኢንስታግራም በግዛቷ እንዳይሰራ እግድ መጣሏን የሀገሪቱ የኢንፎቴክ ተቆጣጣሪ በዛሬው እለት አስታውቋል።
ተቆጣጣሪው አካል እግድ የጣለበትን እና እግዱ እስመቼ እንደሚቆይ ግልጽ አላደረገም።
ይህ እርምጃ የተወሰደው የቱርክ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ፋህረቲን አልቱን ለፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ወሳኝ የሆነውን እስማኤል ሀኒየህ ግድያን አስመልክቶ የወጡ የሀዘን መግለጫዎች ኢንስታግራም አጥፍቷል ሲሉ ባለፈው ረቡዕ ትችት ከሰነዘሩ በኋላ ነው።
“ይህ ግልጽ እና ቀላል ነው፤ ሀሳብን መገደብ ነው” ያሉት የቱርክ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አልቱን ኢንስታግራም ለዚህ ድርጊቱ የተጣሰ ፖሊሲ ስለመኖሩ አልጠቀሰም ብለዋል።
የኢንስታግራም እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ በእግዱም ሆነ በአልቱን አስተያየት ዙሪያ የሰጠው አስተያየት የለም።
AL AIN
More Stories
የማህበራዊ ሚዲያው ተፅዕኖ የጎላበት ምህዳር ተፈጥሯል- የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ።
የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች ተልዕኮቸውን በሀላፍነት እና በዕውቀት እንዲወጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ።
የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ በድህረገጽና በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።