14 የካናዳ ትምህርት ቤቶች በ4 ግዙፍ የማህበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎች ላይ ክስ መስርተው የ8 ቢሊዮን ዶላር ከሳ ጠይቀዋል።ክሱ የተመሰረተባቸው ኩባንያዎች ቲክቶክ፣ ስናፕቻት፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ናቸው።የ14ቱ ትምህርት ቤቶች ቦርዶች አራቱን ኩባንያዎች የከሰሷቸው የተማሪዎችን የአዕምሮ ጤና ጎድተዋል በሚል መሆኑን ቶሮንቶ ስታር ዘግቧል።ቦርዶቹ በኩባንያዎቹ ላይ በፍርድ ቤት ክስ ከመሰረቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት በተጠቀሱት ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚንሸራሸሩ ሀሳቦች “የህጻናትን አስተሳሰብ፣ ባህርይ እና የትምህርት አቀባበል ቀይረዋል” ብለዋል።በኦንታርዮ ግዛት ውስጥ የሚገኙ ከ1 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን የሚወክሉት የ14ቱ ትምህርት ቤቶች ቦርዶች በተማሪዎች የአዕምሮ ጤና እና ደህንነት ላይ የደረሰው ጉዳት ካሳ ያስፈልገዋል ብለዋል።ሁሉም ቦርዶች ከአራቱ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከካሳ ክፍያው በተጨማሪ በቀጣይ በተማሪዎች ላይ የሚሳድሩትን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ የሚያስችሉ ትላልቅ ለውጦችን እንደሚጠብቁ ጠቁመዋል። ፌስቡክ እና ኢንስታግራምን የሚያስተዳድረው የሜታ ኩባንያ ቃል አቀባይ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም “የታዳጊዎችን ደህንነት የማይፃረሩ፣ ይልቁንም አጋዥ የሆኑ፣ የወላጆችንም ፍላጎት የሚያከብሩ ተሞክሮዎችን የሚያጋሩ ናቸው” ብለዋል።ይሁን እንጂ ይህ የኩባንያው ምላሽ በቦርዶቹ ተቀባይነት አላገኝም። ልጆቻችን አዕምሯቸው፣ ውሏቸው እና የትምህርት አቀባበላቸው የተቀየረው እነዚህ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከተስፋፉ በኋላ ነው ብለው ያምናሉ።ከካናዳ በተጨማሪ ወደ 500 የሚጠጉ የአሜሪካ ትምህርት ቤቶች ቦርዶችም በኩባንያዎቹ ላይ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበዋል ሲል የዘገበው ቲአርቲ ወርልድ ነው።
Al-Ain
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ