በ2016 በጀት ዓመት በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ከሙስና እና ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የፌደራል የስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ ።
በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው÷ በ2016 በጀት ዓመት በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም÷ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ175 ሺህ በላይ አመራርና ሰራተኞች ሃብታቸውን ማስመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡
በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 1 ሺህ 87 አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ መከናወኑን ነው የተናገሩት፡፡
በዚህም 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር እና 8 ሺህ 490 የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን ጠቁመው÷ ከመሬት ጋር በተያያዘም ከ46 ሚሊየን ካሬ ሜትር የከተማና የገጠር ቦታ ከሙስና ምዝበራ ማዳን ተችሏል ብለዋል፡፡
አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራው ከግዥ፣ መሬት አሰጣጥ፣ ንብረት ማስወገድ፣ ገቢ አሰባሰብ ፣ ዕርዳታ አሰጣጥ እና ከማዳበሪያ ስርጭት ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።