በካሜሮን ዱዋላ ከተማ በሚደረገው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ለሚካፈለው የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በዛሬው ዕለት ሽኝት ተደርጓል።
በ23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከተዘጋጁት 45 የሜዳ ላይ ተግባራት ኢትዮጵያ በ41ዱ የምትሳተፍ ሲሆን÷34 ሴት እና 43 ወንድ አትሌቶችም ኢትዮጵያን ወክለው ይሳተፋሉ።
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ እንደገለጹት÷ የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንደ ኦሊምፒክ ላሉ ውድድሮች መነሻ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶችን ለማብቃት ላደረገው ጥረት ሊመሰገን እንደሚገባም አንስተዋል፡፡
የእያንዳንዱ አትሌት ምኞት ውጤት ማምጣትና ኦሊምፒክ ላይ መሳተፍ በመሆኑ እንደ አፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ያሉት ውድድሮች ትልቅ መነሻ ናቸው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በበኩሏ÷ አትሌቶች በቆዩበት የ15 ቀናት የልምምድ ጊዜ እርስ በርስ ለመተዋወቅ እንደረዳቸው ተናግራለች፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።