ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ እንደሚከናወን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
መርሐ-ግብሩን ያዘጋጁት÷ የሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና የትምህርት ሚኒስቴር መሆናቸው ተጠቁሟል።
የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የማዕድ ማጋራት፣ ትምህርትና የጤና አገልግሎት፣ አቅመ ደካሞችን መደገፍ ጨምሮ በዘንድሮው መርሐ-ግብር በ14 መስኮች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል፡፡
በመርሐ-ግብሩ 40 ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎች እንደሚሳተፉ፤ በዚህም ከ21 ቢሊየን ብር በላይ የሚተመን አገልግሎት እንደሚሰጥ እና ከ50 ሚሊየን በላይ ወገኖች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተብራርቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2016 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማስጀመራቸው ይታወሳል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች