ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የ2016 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ እንደሚከናወን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
መርሐ-ግብሩን ያዘጋጁት÷ የሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና የትምህርት ሚኒስቴር መሆናቸው ተጠቁሟል።
የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የማዕድ ማጋራት፣ ትምህርትና የጤና አገልግሎት፣ አቅመ ደካሞችን መደገፍ ጨምሮ በዘንድሮው መርሐ-ግብር በ14 መስኮች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል፡፡
በመርሐ-ግብሩ 40 ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎች እንደሚሳተፉ፤ በዚህም ከ21 ቢሊየን ብር በላይ የሚተመን አገልግሎት እንደሚሰጥ እና ከ50 ሚሊየን በላይ ወገኖች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተብራርቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2016 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማስጀመራቸው ይታወሳል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።