የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኘው የምክክር ምዕራፍ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ተሳታፊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ለመሆኑ እነዚህ የባለድርሻ አካላት ወኪሎች የትኞቹን አካላት ወክለው እየተሳፉ ይገኛሉ?
1. የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች
• ከየወረዳው የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እንዲወክሉ የተመረጡ ተወካዮች
2. የፓለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች
• በአዲስ አበባ ከተማ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የፓለቲካ ፓርቲዎች
3. የተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ የተመዘገቡ)
• የሃይማኖት ተቋማት
• ሲቪል ማህበራት
• የአሰሪዎች ማህበራት
• የሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን
• የመምህራን ማህበር
• የአካል ጉዳተኞች ማህበራት
• የሙያ ማህበራት
• የቀድማው ሰራዊት ማህበር (ተቀናሽ ሰራዊት ማህበር)
• የጋዜጠኞች ማህበር
• የዩኒቨርሲቲ መምህራን (የመንግስት እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት)
• የንግድ ማህበራት ምክር ቤት
• የሴቶች እና ወጣቶች ማህበራት
4. የመንግስት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለው ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ)
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ዳኞች
• የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች
• የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን
5. ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተወካዮች
• በተለያዩ ዘርፎች በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያላቸው፣ አንቱታን ያተረፉ እና ተፅዕኖን መፍጠር የሚችሉ ግለሰቦች
More Stories
በቴፒ ከተማ ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የመሶብ አንድ ማዕከል ከእንግልትና ከምልልስ እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ