በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር” የሚል ቃል አለ፤ ይህን መሰረት ብናደርግ እኛም እርስ በእርሳችን መነጋገራችን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና አስፈላጊ እንደሆነ የሚያሳየን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ኅብረት ፕሬዚዳንትፓስተር ጻዲቁ አብዶ ገለጹ።የኅብረቱ ፕሬዚዳንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ከኢቢሲ ሳይበር ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ ጥበበኞች ዘመኑን የሚያውቁ (የሚመክሩ) ‘ይሳኮር’ የሚባሉ ወገኖች እንደነበሩ ተናግረዋል።”ምክር በሰው ልብ እንደጠሊቅ ውኃ ነው፤አዕምሮ ያለው ሰው ግን ይቀዳዋል”ይላል መፅሐፉ የሚሉት ፓስተር ጻዲቁ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የሚያካትት በመሆኑ ያላግባቡን ጉዳዮች ላይ በግልጽ መወያየት አስፈላጊ ነው ይላሉ፡፡”ኢትዮጵያውያን ለብዙ ሺህ ዘመናት በጎውንም ክፉውንም አይተናል ፤ አሁን ላይ ያሉ አለመግባባቶችን ሁሉ ወደ ጠረንጴዛ በማምጣት እና ሀገርን በማስቀደም ልንመክር ይገባል” ብለዋል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች