ግዙፉ የአውሮፕላን አማራች ኩባንያ ቦይንግ፤ የአፍሪካ ዋና መቀመጫውን በኢትዮጵያ ሊከፍት መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ የኩባንያው ውሳኔ ተቋሙ ዋና መቀመጫውን በኬኒያ አሊያም በደቡብ አፍሪካ ሊያደርግ እንደሚችል ሲሰጡ የነበሩ ግምቶችን ያስቀረ እና ኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርጫው መሆኗን ያረጋገጠ ነው፡፡ እ.አ.አ በ2023 ኢትዮጵያ እና ቦይንግ ኩባንያ የተወሰኑ የአውሮፕላን ክፍሎችን ኢትዮጵያ ውስጥ ለማምረት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አየር መንገዶች በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አዳዲስ አውሮፕላኖችን እንደሚፈልጉ የኩባንያው ጥናት ያመላክታል፡፡ ከእነዚህ ወስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት አዳዲስ አውሮፕላኖች የአየር መንገዶቹን መዳረሻ ለማስፋት እንደሚያገለግሉ ዲደብሊው አፍሪካ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።