ግዙፉ የአውሮፕላን አማራች ኩባንያ ቦይንግ፤ የአፍሪካ ዋና መቀመጫውን በኢትዮጵያ ሊከፍት መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ የኩባንያው ውሳኔ ተቋሙ ዋና መቀመጫውን በኬኒያ አሊያም በደቡብ አፍሪካ ሊያደርግ እንደሚችል ሲሰጡ የነበሩ ግምቶችን ያስቀረ እና ኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርጫው መሆኗን ያረጋገጠ ነው፡፡ እ.አ.አ በ2023 ኢትዮጵያ እና ቦይንግ ኩባንያ የተወሰኑ የአውሮፕላን ክፍሎችን ኢትዮጵያ ውስጥ ለማምረት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አየር መንገዶች በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አዳዲስ አውሮፕላኖችን እንደሚፈልጉ የኩባንያው ጥናት ያመላክታል፡፡ ከእነዚህ ወስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት አዳዲስ አውሮፕላኖች የአየር መንገዶቹን መዳረሻ ለማስፋት እንደሚያገለግሉ ዲደብሊው አፍሪካ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።