ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በደረሰው አሰቃቂ የሄሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸውን ላጡት የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር አብዱላሂ በኢትዮጵያ ሕዝብ፣ መንግስትና በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ለፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና አሚር አብዱላሂ ቤተሰቦች እንዲሁም ለኢራን ሕዝብና መንግስትም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።