ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በደረሰው አሰቃቂ የሄሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸውን ላጡት የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር አብዱላሂ በኢትዮጵያ ሕዝብ፣ መንግስትና በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ለፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና አሚር አብዱላሂ ቤተሰቦች እንዲሁም ለኢራን ሕዝብና መንግስትም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
FBC
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ