በጃፓን እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ፓራ-አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡በሻምፒዮናው በአራት የጉዳት ዘርፎች ከተሳተፉ አትሌቶች መካከል ትዕግስት ገዛኸኝ በ1 ሺህ 500 ሜትር (ቲ13 ቡድን) በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡አትሌት ትዕግስት ርቀቱን ያጠናቀቀችበት 4 ደቂቃ 18 ሰከንድ 90 ማይክሮ ሰከንድ የዓለም ሪከርድ ሆኖ መመዝገቡም ተመላክቷል፡በሌላ በኩል አትሌት ያየሽ ጌጤ የ1 ሺህ 500 ሜትር (ቲ11 ቡድን) ሩጫ ውድድርን በ4 ደቂቃ 31 ሰከንድ 77 ማይክሮ ሰከንድ ሪከርድ በመስበርና በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን ችላለች፡፡
FBC
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ