የኢራኑን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይስን ጨምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱን ባለስልጣናት አሳፍሯል” የተባለ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር በምሥራቅ አዘርባጃን መከስከሱን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡እንደ ቴህራን ታይምስ ዘገባ በበረራ ላይ የነበሩት ሦስት ሄሊኮፕተሮች ሲሆኑ ሁለቱ በመዳረሻቸው አርፈዋል፡፡በሌላ በኩል “በተከሰከሰው ሄሊኮፕተር ውስጥ የኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አሚር አብዶላህያን፣ የአያቶላህ አል ሀሺም መስጂድ ኢማም እና የምሥራቅ አዘርባጃን ግዛት አሥተዳዳሪ ማሌክ ራህማቲ ሳይሳፈሩ እንዳልቀሩ” ግምታዊ ዘገባዎች እየወጡ ነው፡፡ይሁን እንጂ በተከሰከሰው ሄሊኮፕተር ውስጥ በትክክል እነማን ተሳፍረው እንደነበር ጥርት ያለ መረጃ አለመኖሩ የተመላከተ ሲሆን÷ የሄሌኮፕተሩ አደጋ መንስኤ ምን እንደሆነም ማብራሪያ አለመኖሩን ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ዘግቧል፡፡ፕሬዚዳንት ራይሲ ዛሬ በምሥራቃዊ አዘርባጃን ግዛት ተገኝተው የቂዝ ቃላሲ ግድብን መርቀው በመመለስ ላይ ሳሉ የተሳፈሩበት ሄሊኮፕተር ሳይከሰከስ እንዳልቀረ ዘገባዎች አመላክተዋል፡፡
FBC
More Stories
የአሜሪካ ወታደሮች ላይ የተሰነዘረውን የጥቃት ሙከራ ተከትሎ ዋሽንግተን ኢራን ላይ “ከፍተኛ” ጥቃት ፈጸመች
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ከ37 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ተገለፀ::
አሜሪካ የመርከቦችን እንቅስቃሴ እያወኩ ነው ባለቻቸው የኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ አዲስ ጥቃት ፈጸመች፡፡