በአዘርባጃን በይፋዊ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአገሪቱ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሚካይል ጃባሮቭ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።በውይይቱም የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።በኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ የመልማት ጸጋ እና ዕድል ለመጠቀም፣ በተለይም ገቢን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት አዘርባጃን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ሚካይል ጃባሮቭ ገልጸዋል። በኢንቬስትመንትና በስትራቴጂያዊ ስራዎች ያላትን ልምድ ለማካፈልም አገሪቱ ፍላጎት እንዳላት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።በተጨማሪም አገሪቱ በጋራ መልማት የሚያስችሉ ዕድሎችን ሁሉ ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …