የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ፎረም “ከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ውጤት” በሚል መሪ ሀሳብ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል።ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ፎረም ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራት እየተከናኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ሚኒስትር ዴኤታው፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።የጥራት፣ የመልካም አስተዳደር እና የገንዘብ ድጋፍ ችግሮች ተቋማቱን እየፈተ ስለመሆኑ ነው የጠቆሙት።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤የትምህርት ስርዓቱን ለመቀየር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።
EBC
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ