የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት፣ የክልል የዘርፉ አስፈፃሚዎችና ባለድርሻ አካላት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ በአዳዲስ ኢንቨስትመንት ማስፋት፣ በኢንዱስትሪ ሽግግር፣ በጥናትና ምርምር ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በመድረኩ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የዘርፉ ሞተር በማድረግ ዘርፉን ለማነቃቃት በታቀደው መሠረት የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡በዚህም የአምራች ኢንዱስትሪ ዋነኛው ሀገራዊ የርብርብ ማዕከል እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች