
ኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚፈልጉ ተገለጸ፡፡በኳታር፣ የመን እና ኢራን የኢፌዲሪ አምባሳደር ፈይሰል አልይ ከኳታር የኢንቨስትመንት ባለስልጣን የአፍሪካ ዳይሬክተር ሱልታንአል ሳዓዲ እና ልዑካቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡አምባሳደር ፈይሰል÷ በኢትዮጵያ በሆቴል ቱሪዝም፣ በታዳሽ ኃይልና በአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት ዘርፍ የውጭ ኩባንያዎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡የኳታር ኢንቨስትመንት ባለስልጣን የሀገሪቱ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ ሱልታንአል ሳዓዲ በበኩላቸው÷ የኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መናገራቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
በቴፒ ከተማ ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የመሶብ አንድ ማዕከል ከእንግልትና ከምልልስ እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ