
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ናታኒያሁ ዛሬ በኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) ባጋሩት መረጃ፥ ካቢኔያቸው በእስራኤል የሚገኘውን የአልጀዚራ ቢሮ ለመዝጋት ከውሳኔ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። እንደ አሶሼትድ ፕሬስ ዘገባ፥ ውሳኔው በአልጀዚራ ላይ ስለሚኖረው ተፅዕኖ እና መቼ ተግባራዊ እንደሚደረግ ግን የተባለ ነገር የለም፤ ውሳኔው ዘላቂ ይሁን ጊዜያዊም የታወቀ ነገር የለም።ውሳኔው በእስራኤል እና በአልጀዚራ መካከል የቆየውን ቁርሾ እንደሚያባብሰው ይጠበቃል።የአልጀዚራ ቻናል ባለቤት የሆነችው ኳታር የጋዛን ጦርነት ለማስቆም እየተደረገ ባለው ጥረት ቁልፍ ሚና እየተጫወተች መሆኑ ይታወቃል።በመሆኑም በዚህ ሰዓት የተላለፈው የእስራኤል ካቢኔ ውሳኔ በሁለቱ አገረት መካከል ውጥረት እንዳያነግስ ተሰግቷል። እስራኤል እርሷን በተመለከተ የተዛቡ ዘገባዎችን ያሰራጫል የምትለውን አልጀዚራን ከሀማስ ጋር በማበር ጭምር ትከሰዋለች። አልጀዚራ በጦርነቱ ወቅት ጋዛን ለቀው ካልወጡ ጥቂት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች አንዱ ነው።ቻናሉ አሰቃቂ የአየር ጥቃት እና የሆስፒታል ትዕይንቶችን ከጋዛ በቀጥታ ሲዘግብ እና እስራኤልን በጅምላ ጭፍጨፋ ሲከስ ቆይቷል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች