መሬት ያለ እረፍት በደቂቃ 27.7 ኪሎ ሜትር (በሰዓት ከ1,600 ኪሎ ሜትር በላይ) በራሷ ዛቢያ ላይ ትሽከረከራለች። እስቲ አስቡት፤ ይህን ያህል ፍጥነት እያላት በድንገት “ቆም” ብትል ምን ሊፈጠር ይችላል? ውጤቱ አስከፊና ምናባዊ ከሚመስል አደጋ በላይ ነው።
ልክ በከፍተኛ ፍጥነት እየተጓዘ ያለ መኪና ድንገት ፍሬን ሲይዝ በውስጡ ያለ ሰው ወደ ፊት እንደሚወረወረው ሁሉ፣ መሬትም በድንገት ብትቆም በላዩዋ ላይ ያለን እኛ ሰዎች፣ ቤቶች፣ ተሽከርካሪዎች እና ተራራዎች ጭምር በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ምስራቅ አቅጣጫ እንወረወራለን።
መሬት ወደ ምስራቅ እየተጓዘች በመሆኑ፣ እርሷ ብትቆምም እኛ ግን በነበረን ፍጥነት ጉዟችንን ስለምንቀጥል ከመሬት አካል ላይ ተፈንጥረን እንወጣለን።
አደጋው በዚህ ብቻ አያበቃም፤ የውቅያኖስ ውሃዎች ሁሉ ካሉበት ተነቅለው ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ግዙፍ ማዕበልና ሱናሚ ምድርን ያጥለቀልቋታል። መሬት ለአንድ ዓመት መሽከርከር ብታቆም ደግሞ ወቅቶችና የሌሊትና ቀን ዑደት ይናጋል።
ለስድስት ወራት ያህል በአንድ በኩል ያለው የምድር ክፍል የፀሐይ ንዳድ ውስጥ ስለሚቆይ ይቃጠላል፤ ቀሪው ስድስት ወር ደግሞ በሌላኛው በኩል ድቅድቅ ጨለማና የማይቻል ቅዝቃዜ (በረዶ) ይነግሳል።
መሬት ያለ እረፍትና በጥንቃቄ መሽከርከሯ ለእኛ ለሰው ልጆች ህልውና የተሰጠ ትልቅ ስጦታ መሆኑን የሳይንስ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
More Stories
ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ተሾሙ
ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ የጠፈር ጣቢያዋን ለውጭ ሀገር ጠፈርተኞች ክፍት አደረገች