በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ሂልተን ሆቴል በተካሄደው የኋይት ሃውስ የዘጋቢዎች ማኅበር ዓመታዊ የእራት ግብዣ ላይ፣ የተኩስ ድምጽ በመሰማቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በደህንነት አባላት ታጅበው በአስቸኳይ ከመድረክ እንዲወጡ ተደርጓል።
በወቅቱ በስፍራው የነበሩት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ እና በርካታ የካቢኔ አባላትም በፍጥነት ከአካባቢው ተወስደዋል።
የአሜሪካ የደህንነት አገልግሎት ባወጣው መግለጫ፣ ፕሬዝዳንቱ እና ምክትል ፕሬዝዳንቱ ደህንነታቸው የተጠበቀ መሆኑንና አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በ’ትሩዝ ሶሻል’ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተኳሹ መያዙን ገልጸው ለህግ አስከባሪዎች ፈጣን እና ደፋር እርምጃ ምስጋና አቅርበዋል።
በስፍራው የነበሩት የሲኤንኤን ጋዜጠኞችም ተኳሹ በጥቂት እርምጃዎች ርቀት ላይ እንደነበር የገለጹ ሲሆን፤ ድርጊቱ እጅግ አስደንጋጭ እንደነበር ዘግበዋል።
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ተሾሙ
ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ የጠፈር ጣቢያዋን ለውጭ ሀገር ጠፈርተኞች ክፍት አደረገች
ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የሚላመድና የማይበገር የልማት ግስጋሴዋን በተጨባጭ ውጤቶች እያስመሰከረች ቀጥላለች።