
የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዡዩአን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደመላሽ ገ/ሚካኤል፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች አመራሮችም ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡በኢትዮጵያ የነበራቸው የሥራ ጊዜ ስኬታማ እንደነበር የገለጹት አምባሳደር ዣኦ ዡዩአን÷በሁለቱ ሀገራት ያለው ትብብር 50 ዓመታትን ከመሻገሩ ባለፈ ወደ ስትራቴጂያዊ አጋራነት ማደጉን ጠቅሰዋል።አምባሳደሩ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል፡፡በሥራ ቆይታቸው በቻይና መንግስት ድጋፍ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የነበሩ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ለፍጻሜ መብቃታቸው ተጠቁሟል፡፡ኢትዮጵያ ብሪክስን እንድትቀላቀል ቻይና ያደረገችው ድጋፍ የሁለቱ ሀገራት የረዥም ዘመን ጠንካራ ወዳጅነት ሌላኛው ማሳያ መሆኑም ተወስቷል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።