ኢራን የፓኪስታን ሰንደቅ ዓላማ የያዙ 20 ተጨማሪ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እንዲያልፉ ፈ
ኢራን በፓኪስታን ስም የተመዘገቡ 20 ተጨማሪ መርከቦች ለሳምንታት ተዘግቶ በቆየው የሆርሙዝ ሰርጥ በኩል እንዲያልፉ መስማማቷን ፓኪስታን አረጋገጠች።
የፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢሻቅ ዳር ይህንኑ ውሳኔ በ‘ኤክስ’ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ያረጋገጡ ሲሆን፣ “እርምጃው የሚደነቅ እና ገንቢ ነው” ብለዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም “ይህ የኢራን እርምጃ የሰላም አብሳሪ እና በቀጣናው መረጋጋትን ለማምጣት የሚረዳ ነው፤ ውይይት፣ ዲፕሎማሲ እና መሰል መተማመንን የሚፈጥሩ እርምጃዎች ለጦርነት ብቸኛ መፍትሔዎች ናቸው” ብለዋል።
ፓኪስታን በመካከለኛው ምሥራቅ ግጭት ዙሪያ ዛሬ (እሑድ) የሚካሄደውን የአራትዮሽ ስብሰባ ለማስተናግድ መርሐ-ግብር ይዛለች።
በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት አንድ ወር በደፈነበት በዚህ ወቅት፣ የቱርክ፣ የፓኪስታን፣ የግብፅ እና የሳዑዲ ዓረቢያ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በኢስላማባድ በመገኘት፣ ውጥረቱን ለማርገብ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ይመክራሉ።
የሆርሙዝ ሰርጥ የዛሬ ወር ገደማ በተቀሰቀሰው የአሜሪካ-እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ምክንያት ከፈረንጆቹ መጋቢት ወር መጀመሪያ አንሥቶ በተግባር ተዘግቶ ቆይቷል።
ግጭቱ ከመከሰቱ በፊት በቀን በአማካይ 138 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል ያልፉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ።
More Stories
ኢራን በእስራኤል የኢንዱስትሪ ማዕከል ላይ የሚሳዔል ጥቃት ፈጸመች
ሩሲያ ከመጋቢት 23 ጀምሮ የነዳጅ (ቤንዚን) ኤክስፖርት ልታግድ ነው።
የሁቲ ሁለተኛ ዙር ጥቃት እና የአሜሪካ እግረኛ ጦር…