ማሻ፤ የካቲት 24/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ የፓርቲው አባላትና አመራሮች 7ኛውን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በጌጫ ከተማ ሰጥቷል
ፓርቲው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ”ሰላም ለሁሉም ፤ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ፖለቲካዊ ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለአባላቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በመድረኩ የተገኙት በሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ገቦ እንደተናገሩት ፓርቲው በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመጣመር እየተፎካከረ ይገኛል ብለዋል።
ምርጫው ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ፓርቲው እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል አቶ ዮሐንስ።
ጥምረቱ የተፎካካሪነት አቅም እንዲጎለብት ያግዛል ያሉት አቶ ዮሐንስ የተለያዩ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በዝርዝር አቅርበዋል።
የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት አቶ አዲሱ አምበሎ በበኩላቸው የፓርቲው አመራሮችና አባላቱ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እንዲሳተፉና በፓርቲው የተለያዩ እሳቤዎች ዙሪያ ግንዛቤ እንዲጨብጡ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል።
የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የመወዳደሪያ ምልክት ቡና ሲሆን እርግብ የጥምረቱ አርማ መሆኑም ተገልጿል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።