ማሻ፤ የካቲት 22/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) አትሌት ታደሰ ታከለ የ2026 የቶኪዮ ማራቶን አሸናፊ ሆኗል።
አትሌቱ በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒዬም ደረጃ በተሰጠው እና ለ19ኛ ጊዜ የተደረገውን የቶኪዮ ማራቶን በቀዳሚነት ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ37 ሴኮንድ ፈጅቶበታል።
አትሌት ታደሰ ታከለ የባለፈው ዓመት ውድድርም አሸናፊ እንደነበር አይዘነጋም።
በውድድሩ አትሌት ሙክታር እድሪስ 5ኛ፣ሰለሞን ባረጋ ደግሞ 7ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
በሴቶች ማራቶን አትሌት ብርቱካን ወልዴ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ ሀዊ ፈይሳ ሦስተኛ እንዲሁም አትሌት ሱቱሜ አሰፋ አራተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
ውድድሩን ኬንያዊቷ አትሌት ብሪጅ ኮስጊ በቀዳሚነት አጠናቃለች።
More Stories
አርሰናል እና ባየር ሙኒክ ለግማሽ ፍጻሜ ደረሱ
ፖርተኞች ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነት በመላበስ ውድድር ማካሄድ እንዳለባቸው የዉድድሩ ስነስርዓት ኮሚቴ ገለፀ።
አሜሪካዊቷ የኦሊምፒክ ሻምፒዮን አዲስ አበባ ገባች!