ማሻ፤ የካቲት 22/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) አትሌት ታደሰ ታከለ የ2026 የቶኪዮ ማራቶን አሸናፊ ሆኗል።
አትሌቱ በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒዬም ደረጃ በተሰጠው እና ለ19ኛ ጊዜ የተደረገውን የቶኪዮ ማራቶን በቀዳሚነት ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ37 ሴኮንድ ፈጅቶበታል።
አትሌት ታደሰ ታከለ የባለፈው ዓመት ውድድርም አሸናፊ እንደነበር አይዘነጋም።
በውድድሩ አትሌት ሙክታር እድሪስ 5ኛ፣ሰለሞን ባረጋ ደግሞ 7ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
በሴቶች ማራቶን አትሌት ብርቱካን ወልዴ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ ሀዊ ፈይሳ ሦስተኛ እንዲሁም አትሌት ሱቱሜ አሰፋ አራተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
ውድድሩን ኬንያዊቷ አትሌት ብሪጅ ኮስጊ በቀዳሚነት አጠናቃለች።
More Stories
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
ፒኤስጂ በተከታታይ ለ2ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ
ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ!