ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየምን አስጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለነፃነት ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች ታሪክ ለፕሬዚዳንቱ ተብራርቶላቸዋል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባተላለፉት መልዕክት፤ ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ለነበራቸው ቆይታ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አያይዘውም ፕሬዚዳንቱ በምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚኖራቸው ቆይታ ፍሬያማና ስኬታማ እንዲሆን በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር እንደሆነም ታምኖበታል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።