ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ አካሂዷል ።
የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌታቸው ኬኒ በወቅቱ እንደገለፁት ምክር ቤቱ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አግባብ የብሔረሰቦች የጋራ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል ።
በክልልሉ ውስጥ የሚገኙ ብሔረሰቦች ባህል ፣ታሪክ፣ ቋንቋ እና መልካም ዕሴቶች እንዲጎለብት ከማድረግ አንፃር ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ያነሱት ዋና አፈ ጉባኤው ባለፍት ስድስት ወራት የተከናወኑ ጠንካራ ተግባራትን በማስቀጠል መስተካከል በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ይደረጋል ሲሉ ጠቁመዋል ።
በክልሉ የሚከሰቱ አለመግባባቶችን ሀገር በቀል የሆኑ እውቀቶችን በመጠቀም የመፍታት ባህል እንዲዳብር የማድረግ ስራዎች ላይ ምክር ቤቱ በስፋት እየሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መሰለ ከበደ ናቸው ።
በግምገማው መድረክ ላይ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፓርት በቀረበበት ወቅት የብሔር ብሔረሰቦች የጋራ መግባባት እንዲፈጠር የሀገር ሽማግሌዎችንና የዘርፉ ባለሙያዎችን በማሳተፍ ሀገር በቀል የሆኑ እውቀቶችን የማጎልበት ስራ መሰራቱ ተጠቁሟል ።
የብሔረሰቦች ባህል ፣ታሪክ፣ ቋንቋ እና መልካም ዕሴቶች እንዲጠናከሩና ሀገር በቀል የሆኑ እውቀቶችን በመጠቀም የተጀመሩ መልካም ዕሴት ግንባታ ስራዎች ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል ።
More Stories
የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን መገንባት የሚያስችል ወሳኝ አጀንዳ ነው – አምባሳደር ሶፊ ፍሮም- ኤመስበርገር
በአሜሪካ በተከሰተ በረዶ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ከ5 ሺህ በላይ በረራዎች ተሰረዙ