ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በጃፓኗ ኦሳካ ከተማ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ 3.6 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ 29 ጥፍጥፍ ወርቆችን ለከተማዋ አስተዳደር በስጦታ አበረከተ።
ጥፍጥፍ ወርቁ በሁለት ሳጥኖች ተደርጎ በከተማዋ አስተዳደር ቢሮ አቅራቢያ በድንገት የተገኘ ሲሆን፣ ለጋሹ ከወርቅ ሳጥኖቹ ጋር ባስቀመጠው አጭር ማስታወሻ፤ ስጦታው በከተማዋ ውስጥ ለሚያረጁ የንጹህ ውኃ ቧንቧዎች ጥገናና ለሕዝብ አገልግሎቶች እንዲውል ፍላጎቱ መሆኑን ገልጿል።
ከተማዋ ለቧንቧዎች ቅያሬ ከፍተኛ በጀት በሚያስፈልጋት ወቅት የተገኘው ይህ ድንገተኛ ስጦታ “የሰማይ ሲሳይ” ተብሏል።
ማንነቱን መግለጽ ያልፈለገው ይህ ግለሰብ ምንም ዓይነት አድራሻም ሆነ ምልክት ያላስቀመጠ ሲሆን፣ የከተማዋ ከንቲባ ለለጋሹ ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
More Stories
የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
በክልሉ የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነት እንዲጠናከር በማድረግ የብሔረሰቦች ፍትሃዊ የጋራ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ፦ አቶ ጌታቸው ኬኒ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን መገንባት የሚያስችል ወሳኝ አጀንዳ ነው – አምባሳደር ሶፊ ፍሮም- ኤመስበርገር