ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በጃፓኗ ኦሳካ ከተማ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ 3.6 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ 29 ጥፍጥፍ ወርቆችን ለከተማዋ አስተዳደር በስጦታ አበረከተ።
ጥፍጥፍ ወርቁ በሁለት ሳጥኖች ተደርጎ በከተማዋ አስተዳደር ቢሮ አቅራቢያ በድንገት የተገኘ ሲሆን፣ ለጋሹ ከወርቅ ሳጥኖቹ ጋር ባስቀመጠው አጭር ማስታወሻ፤ ስጦታው በከተማዋ ውስጥ ለሚያረጁ የንጹህ ውኃ ቧንቧዎች ጥገናና ለሕዝብ አገልግሎቶች እንዲውል ፍላጎቱ መሆኑን ገልጿል።
ከተማዋ ለቧንቧዎች ቅያሬ ከፍተኛ በጀት በሚያስፈልጋት ወቅት የተገኘው ይህ ድንገተኛ ስጦታ “የሰማይ ሲሳይ” ተብሏል።
ማንነቱን መግለጽ ያልፈለገው ይህ ግለሰብ ምንም ዓይነት አድራሻም ሆነ ምልክት ያላስቀመጠ ሲሆን፣ የከተማዋ ከንቲባ ለለጋሹ ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።