ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ኢትዮ ቴሌኮም ከአገር ውስጥ ገበያ ባለፈ አገልግሎቶቹን በቀጠናው በማስፋፋት ለአፍሪካ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ የማበርከት ስትራቴጂካዊ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (AFC) ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳማይላ ዙባይሩ ጋር ተወያይተዋል።
በዚህ ወቅትም የተቋሙን ራዕይና ፍላጎት ጠቅሰው፥ ይህን ዕውን ለማድረግ ጠንካራና የረጅም ጊዜ የፋይናንስ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱ ወቅት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተቋሙ ከዚህ ቀደም የተገበራቸው ስትራቴጂዎች የተቋሙን ጠንካራ የመፈጸም አቅም በተግባር ያረጋገጡ መሆኑን አስረድተዋል
#አራዳ ኤፍ ኤም
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ