ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ስልጠናው የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ከክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡
በስልጠናው የሁለቱም ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ሰልጠናውን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ ኡሮ አስጀምረዋል፡፡
የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ፣ የመንግስት አስተዳደር ፖሊሲ የትኩረት መስኮችና የያዛቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የስልጠና ሰነድ እያቀረቡ ነው፡፡
#ቦንጋ ኤፍ ኤም
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።