የካቲት 9/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በስኮትላንድ የግላስጎው የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው የ22 ዓመቷ ኤሚሊያ ኢቫንስ-ሙንተን፣ የዓለማችን ግዙፉን የጦጣ ቅርጽ ያለው (Sock Monkey) የአሻንጉሊት ቅርፅ በመሥራት ጊነስ ዓለም አቀፍ ክብረ ወሰን ላይ ተመዘገበች።
ይህ ግዙፍ አሻንጉሊት 15 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ ለሥራውም 60 ሜትር ገደማ የሚረዝም ጨርቅ እና የተለያዩ ግብዓቶች ጥቅም ላይ ውለዋል።
ወጣቷ አርቲስት ሥራውን የሠራችው ትልልቅ ሰዎች ከግዙፉ አሻንጉሊት አንጻር ሲታዩ ራሳቸውን እንደ ሕፃን እንዲቆጥሩና የልጅነት ስሜታቸው እንዲቀሰቀስ ለማድረግ እንደሆነ ገልጻለች።
ይህ ግዙፍ አሻንጉሊትበእንግሊዝ ኖርፎልክ በተካሄደ የጥበብ ፌስቲቫል ላይ ለሕዝብ የቀረበ ሲሆን፣ ጎብኚዎች አሻንጉሊቱን በመንካት እየተጫወቱ እንዲዝናኑ ተደርጓል ሲል የዘገበው ዩፒአይ ነው።
More Stories
በቴፒ ከተማ ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የመሶብ አንድ ማዕከል ከእንግልትና ከምልልስ እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ