የማላዊ፣ የብሩንዲ፣ የናይጄሪያ፣ የዛምቢያ እና የኮንጎ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ሚኒስትሮቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን፤ ከጉባኤው አስቀድሞ የካቲት 4 እና 5 ቀን የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት 48ኛው መደበኛ ስብሰባ ይካሄዳል።
ጉባኤው “የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና አስተማማኝ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው።
More Stories
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ ይምረጡኝ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ በአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማ ተካሂደዋል ።
ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።