February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ማሻ፤ ጥር 20/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በተገኙበት በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኤኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል።

በክልሉ እየተከሰተ ያለዉን የመሬትና የተፈጥሮ ሀብት መመናመን እና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የመሬት ፣ የውሃና የሰው ሀብት መጠበቅ ፣ ማልማትና በላቀ ደረጃ በማቀናጀት ጥቅም ላይ ማዋል ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መኾኑ ነዉ።

የ2018 የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ስራ ዉጤታማ ለማድረግ የቅድመ ዝግጀት ስራዎች ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት መከናወኑ ተገልጿል።

የ2018 ዓ.ም የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ትግበራ ከወትሮ በተለየ በልዩ በትኩረትና በከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ እየተከናወነ እንደሚገኝ ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በወረዳው ባኒ ቀበሌ፣ ሸዊ ንዑስ ተፋሰስ እየተካሄደ በሚገኘው ክልላዊ ማብሰሪያ ፕሮግራም የግብርና ሚኒስትር ተወካዮች፣ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት እየተሳተፉ ይገኛል። ዘገባው የክልሉ መ/ኮ ነው