February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 46ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

ማሻ፤ ጥር 15/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት  በዛሬው ዕለት ባካሄደው 46ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል ፡፡

በዚህም መሠረት፦

1ኛ.የቀረቡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ላይ ተወያይቷል። በዚህም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን   በግብርና 27፣ በኢንዱስትሪ 4 እና  በአገልግሎት 2  በአጠቃላይ 1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎችን መርምሮ ወደ  ስራ እንዲገቡ ወስኗል።

2ኛ. መስተዳድሩ ምክር ቤቱ የገቢ ግብር ማሻሻያ  ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ወደ ምክር ቤት መርቷል። እንዲሁም የታክስ አስተዳደር ደንብ መርምሮ አጽድቋል።

3ኛ. መስተዳድር ምክር ቤቱ የገጠር ኮሪደር ሥራዎች ዙሪያ ተወያይቶ አቅጣጫ ማስቀመጡን ከክልሉ መ/ኮ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል