
ትውልዱ በሀገረ መንግስት ግንባታው ላይ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ሲሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) አመላከቱ፡፡
“የምሁራንና ወጣቶች ሚና ለሀገረ መንግስት ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ነው፡፡
በብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ዋና ጽ/ቤት በተዘጋጀው 2ኛ ዙር የፓናል ውይይት፤ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ፈቲ መሃዲ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።
እንዲሁም ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የመጡ ወጣት ምሁራንም በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።
ትውልዱ ከሀገር ተረካቢነት ባለፈ በሀገረ መንግስት ግንባታው ላይ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ያመላከቱት አይሻ (ኢ/ር)፤ ወጣቱ በልማቱ ያለውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በዚህም ሀገርን በሚጠቅሙ እና በሚያሳድጉ እንደ ሜጋ ፕሮጀክቶች እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
ዶክተር ፈቲ በበኩላቸው ወጣቱ እንደ ሀገር ኢትዮጵያን ለመገንባት አስተዋጽኦ ሊያደርግ በሚችልባቸው ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ከዚህም ባለፈ በአፍሪካ ውስጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለመሆንና አፍሪካን ለመምራት በማሰብ መስራት ይገባል ነው ያሉት።
በውይይት እና በሃሳብ ልዕልና የሚያምን ትውልድ መገንባት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች