አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በጉዳት ምክንያት ከቅድመ ውድድር ዘመን ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
የ29 ዓመቱ ካሜሮናዊ ግብ ጠባቂ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከስድስት አስከ ስምንት ሳምንታት ድረስ ከሜዳ እንደሚርቅ ተዘግቧል፡፡
የኦናናን ጉዳት ተከትሎ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ሌላ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ሊገደዱ እንደሚችሉ ቴሌግራፍ አስነብቧል፡፡
ኦናና በፈረንጆቹ 2023 ከኢንተር ሚላን ማንቼስተር ዩናይትድን ከተቀላቀለበት ጊዜ ጀምሮ በተደጋጋሚ በሚሰራቸው ስህተቶች ትችት ሲያስተናግድ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ በዚህ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ ጨምሮ ከተለያዩ ግብ ጠባቂዎች ጋር ስሙ በስፋት ሲነሳ ቆይቷል፡፡
More Stories
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
ፒኤስጂ በተከታታይ ለ2ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ
ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ!