ማሻ ፣ የሰኔ 30፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በሸካ ዞን የኪ ወረዳ አላሞ ቀበሌ ከ37 ሚለዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾ ተመርቆ ክፍት ሆኗል ።
ፕሮጀክቱ ከ66 ሄክታር በላይ ማሳ ማልማት እንደሚችልና 1መቶ 60 በላይ አባዎራዎችን ተጠቃሚ እንደምያደረግ ነው የተገለጸው ።
በተጨማሪ በዞኑ ቴፒ ከተማ ላይ በመንግስት እንዲሁም በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባው የጎጅ ድልድይን ጨምሮ ሌሎችም ፕሮጀክቶች እንደምመረቁ ነው የተጠቆመው ።
በዚህ የምረቃ ፕሮግራም ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾን ጨምሮ የክልል፣ የዞን ፣የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል ።
አስቻለው አየለ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች