ማሻ ፣ የሰኔ 30፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በመርሃ ግብሩ የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች እና የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
እንደ ሀገር ጽዱ ኢትዮጵያ ፣ጽዱ አካባቢ መረሃ ግብር ተቀርጾ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ሰነባብቷል ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም ይህ ኢኒሼቲቭ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ እየተከናወነ ይገኛል።
የዚሁ አካል የሆነው አካባቢን የማጽዳት ስራዎችን በማከናወን ለነዋሪዎች ምቹ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በዞኑ ቴፒ ከተማ አስተዳደር ህብረት ቀበሌ የሚገኙ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በማለዳ ወጥተው አጽድተዋል።
በአካባቢ ጽዳት የተሳተፉ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት ከቤት ጀምረው አካባቢያቸውን በጋራ የማጽዳት ስራዎችን አጠናክረው እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል ።
በዚህም በአከባቢው የወባ በሽታ ስርጭት ከባለፈው ወዲህ በእጅጉ እየቀነሰ መምጣቱንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል ።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዋሲሁን አውሎ በሰጡት አስተያየት በከተማው ባሉ 3 ቀበሌዎች የአካባቢ ጽዳት ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
በየሳምንቱ ህዝቡ ወጥቶ አካባቢውን በማጽዳቱ የወባ በሽታ ስርጭት እየቀነሰ መምጣቱንም አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል ።
ህብረተሰቡ የጀመረውን የአካባቢ ጽዳት ስራ የበለጠ በማጠናከር አካባቢውን ጽዱ ማድረግ እንደሚገባቸውም አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል ።
በጽዳት ስራው የቀበሌው ነዋሪዎች ፣የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ