ማሻ ፣ የግንቦት 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ሀገሪቱ ያላት የዉሃ ሀብት ከኢትዮጵያ አልፎ ለአጎራባች ሀገራት ተደራሽ እየሆነ መምጣቱን የዉሃና ኢንጂነር ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ተናገሩ።
በዉሃና ሀይድሮ ዲፕሎማሲ ላይ ትኩረት ያደረገ ምክክር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
ሚኒስትሩ በዚህን ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከ1 መቶ 20 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሊትር በላይ የዉሃ ሀብት ቢኖራትም ባላት ሀብት ልክ እየተጠቀመች አይደለም።
በመሆኑም ቀጥሎ ባሉት ጊዜያቶች ያሉትን የዉሃ ሀብቶች በሚገባ በመጠቀም የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ለዚህም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በምክክሩ የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ፋና
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።