ማሻ ፣ የግንቦት 12፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ወረዳው ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል ።
በበልግ አዝመራዉ በእንሰት፣በቦቆሎ፣በድንች፣በአተክልትና ፍራፍሬ እንድሁም በቦሎቄ ከ8 ሺህ 656 ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ 6ሺህ 932 ሄክታር መሸፈን መቻሉን የአንድራቻ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አክልሉ ሸነኖ አስታዉቋል።
ወረዳዉ ለእንሰት ተክል በሰጠዉ ትኩረት በ3 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ 12 ሚሊየን የእንሰት ችግኝ ለመትከል አቅዶ በ2 ሺህ 687 ሄክታር መሬት ላይ በተለያዩ ደረጃ የሚገኙ 9ነጥብ 5 ሚሊየን የእንሰት ችግኝ መተከሉንም ገልፀዋል።
ከዕቅዱ ቀሪ 2.5 ሚሊየን የእንሰት ችግኝ በመጪዉ ዓመት በሚተከለዉ ተጨማሪ ሆነዉ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተጠቅሷል።
በበልግ አዝመራ የተተከሉትና የተዘሩ ሰብሎች ውጤታማ ለማድረግ አርሶ አደሩ የአረም ሳምንታትን ተከታትሎ በመቆጣጠርና በመንከባከብ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
ዘጋቢ ግርማ ጮሪቶ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች