ማሻ ፣ የመጋቢት 16፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የሸካ ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤውን መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም በማሻ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል ።
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን ምክር ቤቱ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የተለያዩ ደንቦችን በማፅደቅ ለህዝብ ተጠቃሚነት ክትትልና ቁጥጥር ሲያደርግ እንደቆየ ጠቁመዋል ።
በዚህም በግብርና ዘርፍ፣በከተማ ልማት ከመሬት አቅርቦት ጋር ተያይዞ በርካታ ተግባራት መኖራቸውንና፣በእንሰት ምርት በስድስት ወር ውስጥ የተሻለ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል ።
በመንገድ ዘርፍም የተሻለ ስራ መሰራቱን የገለፁት ዋና አፌ ጉባኤ ለቀጣይ ውጤታማነት የምክር ቤቱ አባላት አቅጣጫ እንዲያስቀምጡ ጠቁመዋል ።
በጉባኤው የባለፈው ጉባኤ ቃለ -ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣የአስፈጻሚ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣የሸካ ማህበረሰብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያ የእስካሁን አፈፃፀምና የቀሪ ወራት የጣቢያው ዕቅድ ቀርቦ ገምግሞ ከማፅደቅ ባለፈ ምክር ቤቱ ሹመትን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚተላለፍም ተናግረዋል ።
በጉባኤው ላይ የሀገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች፣ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም ከሁሉም መዋቅር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
More Stories
የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ በመምህር ዳኪቶ ጋወቶ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ።
ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ
መልካም አብነቶች በማስፋት ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ እናፋጥናለን – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)