ማሻ ፣ የመጋቢት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) በሁቲ አማጺያን በቀይ ባህር ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ካልቆመ አካባቢውን ገሃነም እናደርገዋለን ሲሉ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዝተዋል::
የሁቲ አማጺያን በቀይ ባሕር መርከቦች ላይ ላደረሱት ጥቃት አሜሪካ ከባድ የአየር ድብደባ ማካሄዷን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ የትስስር ገጻቸው ገልፀዋል::
በድብደባው 15 ሰዎች መገደላቸውንና ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸውን በሁቲ የሚመራው የጤና ሚኒስትር አስታውቋል።
በሰንአ እና ሳዳ አካባቢ ተከታታይ የአየር ጥቃት ሲሰማ መዋሉንም ቢቢሲ ዘግቧል።
ፕሬዚዳንቱ በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጺያን በአሜሪካ መርከብ ላይ የሚሳዔል ጥቃት አድርሰዋል ብለዋል::
በጥቃቱም ወታደሮቻቸውና አጋሮቻቸው ዒላማ መሆናቸውን ገልፀዋል::
እስከአሁን በሁቲ አማጺያን የሽብር ድርጊት በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት አጥተናል፤ ሕይወትም አደጋ ውስጥ ወድቋል ብለዋል።
አሜሪካና አጋሮቿ ቀይ ባሕር ላይ የሚደርስ ማንኛውንም ጥቃት ለመከላከል ኃይል ቢያሰማሩም ማስቆም ግን አልቻሉም።
ሁቲዎች እጃቸውን ካልሰበሰቡ አካባቢውን ገሃነም እናደርገዋለን ሲሉ ትራምፕ ዝተዋል::
ሁቲ በምላሹ የአሜሪካ የአየር ጥቃት አሜሪካና አጋሮቿን ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ብሏል::
ኢራን በጉዳዩ ስሟ መነሳቱ አላስደሰታትም::
ፋና
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።