ማሻ ፣ የመጋቢት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) በሁቲ አማጺያን በቀይ ባህር ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ካልቆመ አካባቢውን ገሃነም እናደርገዋለን ሲሉ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዝተዋል::
የሁቲ አማጺያን በቀይ ባሕር መርከቦች ላይ ላደረሱት ጥቃት አሜሪካ ከባድ የአየር ድብደባ ማካሄዷን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ የትስስር ገጻቸው ገልፀዋል::
በድብደባው 15 ሰዎች መገደላቸውንና ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸውን በሁቲ የሚመራው የጤና ሚኒስትር አስታውቋል።
በሰንአ እና ሳዳ አካባቢ ተከታታይ የአየር ጥቃት ሲሰማ መዋሉንም ቢቢሲ ዘግቧል።
ፕሬዚዳንቱ በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጺያን በአሜሪካ መርከብ ላይ የሚሳዔል ጥቃት አድርሰዋል ብለዋል::
በጥቃቱም ወታደሮቻቸውና አጋሮቻቸው ዒላማ መሆናቸውን ገልፀዋል::
እስከአሁን በሁቲ አማጺያን የሽብር ድርጊት በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት አጥተናል፤ ሕይወትም አደጋ ውስጥ ወድቋል ብለዋል።
አሜሪካና አጋሮቿ ቀይ ባሕር ላይ የሚደርስ ማንኛውንም ጥቃት ለመከላከል ኃይል ቢያሰማሩም ማስቆም ግን አልቻሉም።
ሁቲዎች እጃቸውን ካልሰበሰቡ አካባቢውን ገሃነም እናደርገዋለን ሲሉ ትራምፕ ዝተዋል::
ሁቲ በምላሹ የአሜሪካ የአየር ጥቃት አሜሪካና አጋሮቿን ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ብሏል::
ኢራን በጉዳዩ ስሟ መነሳቱ አላስደሰታትም::
ፋና
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች