ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የማጠቃለያ መድረኩን የመሩት የሸካ ዞን ግብርና መምረያ ሀላፍ አቶ አዕምሮ ደሳልኝ እና የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን አዳሾ እንደገለፁት የግብርና ባለሙያዎች አገልግሎት መቀዛቀዝ በግብርና ተግባር ላይ ያሳደረውን አሉታዊ ተፅዕኖን ለመቅረፍ ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችንን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በሀገር ደረጃ የታየውን የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን አዳሾ እንደገለፁት በየዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች የሙያውን መብትና ግደታ በመረዳት ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ በግምገማው የተቀመጡ አቅጣጫዎችንና ትምህርቶችን ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈጻጸም ማሳየት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የግምገማው ውጤት በተመለከተም አጠቃላይ የተገመገሙ ወንድ 67 ሴት 52 በድምሩ 119,የተገመገሙ ሲሆን በማስጠንቀቂያ ወንድ 15 ሴት 10 በድምሩ 25 እና በዲስፕሊን ወንድ 1 እንዲሁም ፤ በህስ ወንድ 51 ሴት 42 በድምሩ 93 ባለሙያዎች እንዲጠየቁ ውሳኔ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል።
በመድረኩም የግብርና ባለሙያዎች ችግር ፈች ድጋፍ ያለማድረግ፣ የኤፍቲስ ማሳዎችን ሞዴል ያለማድረግ ፤ ዉሎአድሮ በቦታው ተተክሎ አለመስራት ፤ የግባዓት አቅረቦ ችግር ፤ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዝቅተኛ መሆን ፤ የሕግ-ወጥ መሬት ወረራን ያለመከላከል ፣ በክህሎትና በባለሙያ የሥራ ሥነ-ምግባር ችግር እንዲሁም በማስፈጸም ረገድ የሚታዩ ውስንነቶች በግምገማ ላይ በሰፊው ተነስቷል።
በመድረኩም የክልል ፣ የዞንና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ጨምሮ የ19ኙ ቀበሌ አስተዳዳሪዎችና የፓይለት አመራሮች እንዲሁም የግብርና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ወረዳ ኮሚኒኬሽን
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።