የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ግድቦች በቂ ውሃ መያዝ ይኖርባቸዋል።
በክረምቱ ወቅት ከፍተኛ የውሃ መጠን ያከማቹ ማመንጫ ጣቢያዎች ከፍተኛ ኃይል እንዲያመነጩ በማድረግ አነስተኛ ውሃ የነበራቸው ግድቦችን የኃይል ጭነት በመቀነስ በተገቢው መጠን ውሃ እንዲይዙ መደረጉን ተናግረዋል።
በአሁኑ ጊዜ ሁሉም ግድቦች የያዙት የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ማሳካት እንደሚያስችል ነው ያመላከቱት።
እንደ ስራ አስኪያጇ ገለፃ፤ ግልገል ጊቤ 1ኛ፣ ፊንጫ፣ መልካ ዋከና፣ ጣና በለስ፣ ተከዜ፣ ገናሌ ዳዋ፣ ቆቃ እና የህዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ግድቦች የሞሉ ሲሆን ጊቤ 3ኛ እና አመርቲ ነሼ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ደግሞ በበቂ ደረጃ ውሃ ይዘዋል፡፡
ግድቦች የያዙትን የውሃ መጠን በአግባቡ ለመጠቀም ከጥገና፣ ከውሃ አስተዳደር እና ከመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ጋር በተያያዘ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ወይዘሮ ጥሩወርቅ አመልክተዋል፡፡
የ2017 በጀት ዓመት የግድቦች የውሃ አያያዝ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር የተሻለ እንደሆነ በዳሰሳ ጥናት መረጋገጡንም ተናግረዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች ከ25 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።