ማሻ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 ሩሲያ በዩክሬን ኢነርጂ መሰረተ ልማቶች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሟን አስታወቀች፡፡
ጥቃቱ ከቀናት በፊት ዩክሬን በሩሲያ ታጋኖርግ ግዛት ለፈጸመችው የሚሳኤል ጥቃት አጸፋ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ዩክሬን ወታደራዊ አቅሟን ለማጠናከር በምትጠቀምበት የነዳጅና የኢነርጅ መሰረተ ልማቶች ላይ የተሳካ ጥቃት ተፈጽሟል፡፡
የዩክሬን ኢነርጂ ሚኒስትር ጀርማን ጋሉሸንኮ በበኩላቸው÷የሀገሪቱ የሃይል መሰረተ ልማት ሞስኮ በፈጸመችው ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት ማስተናገዱን ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ ያደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ የሚፈጠረውን የጎንዮሽ ጉዳት ለመቀነስ ባለሞያዎች ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኙ መጠቆማቸውንምአር ቲ ዘግቧል፡፡
በሌላ በኩል በማህበራዊ ትስስር ገጾች የተሰራጩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንደሚያሳዩት÷በዩክሬን ኦዴሳና ኢቫኖ ፍራንኮቮስክ አካባቢ ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ ከተሰማ በኋላ በአካባቢው የሚገኙ የሃይል መሰረተ ልማቶች በእሳት ተያይዘዋል፡፡
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።