ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) ላይ ለመሳተፍ አዘርባጃን ባኩ ገብተዋል፡፡ፕሬዚዳንቱ ሀይደር አሊየቭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአዘርባጃን ጤና ሚኒስትር ቴይሙር ሙሴየቭን ጨምሮ በከፍተኛ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡”በጋራ ለአረንጓዴ ምድር” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ በሚገኘው የኮፕ29 ጉባዔ ኢትዮጵያ በተራቆተ መሬት የደን ሽፋንን መልሶ ለማልማት የወሰደችውን ቁርጠኝነት እና ዘላቂነት ያለው የመሬት አጠቃቀም ተሞክሮዋን እንደምታቀርብ ይጠበቃል።ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ኢኒሼቲቭ በተለይ በግብርና፣ በኢኮ-ቱሪዝምና በታዳሽ ሀይል ላይ እየተሰራ ያለው ስራ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝም ይታወቃል።
al-Ain
More Stories
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።
ከውሃ ሀብት የሚገኘውን ጥቅም ለማጎልበት መስራት ያስፈልጋል – ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች