ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) ላይ ለመሳተፍ አዘርባጃን ባኩ ገብተዋል፡፡ፕሬዚዳንቱ ሀይደር አሊየቭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአዘርባጃን ጤና ሚኒስትር ቴይሙር ሙሴየቭን ጨምሮ በከፍተኛ ሃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡”በጋራ ለአረንጓዴ ምድር” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ በሚገኘው የኮፕ29 ጉባዔ ኢትዮጵያ በተራቆተ መሬት የደን ሽፋንን መልሶ ለማልማት የወሰደችውን ቁርጠኝነት እና ዘላቂነት ያለው የመሬት አጠቃቀም ተሞክሮዋን እንደምታቀርብ ይጠበቃል።ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ኢኒሼቲቭ በተለይ በግብርና፣ በኢኮ-ቱሪዝምና በታዳሽ ሀይል ላይ እየተሰራ ያለው ስራ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝም ይታወቃል።
al-Ain
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።