በተለይም በሽታው ለመከላከል የትንኝ መራቢያ ቦታዎችን ማፋሰስና ማዳፈን ስራ ላይ ህብረተሰቡ ትኩረት አደርገው እንድሰራ ጽ/ቤቱ አሳስቧል።የኪ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተካልኝ ባሳ እንደገለጹት ለህብረተሰቡ ዋነኛ የጤና ስጋት የሆነውን የወባ በሽታን ለመከላከል የአካባቢ ንጽህና በመጠበቅ ዙሪያ ሰፊ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።እንደ ወረዳ ከ22ቱ ቀበሌዎች 14 የወባ መቀነት ተብሎ በተለዩት አካባቢዎች ግብረ -ኃይ ተቋቁመው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።ወቅቱ ቡና የሚሰበሰብበት በመሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ ከአካባቢው ርቀው ስለሚቆዩ በተለይ ሴቶችና ህጻናት ለበሽታው ስለሚጋለጡ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ኃላፊ ተናግረዋል። የአጎበር አጠቃቀምን በትክክል ተግባራዊ ማድረግ ከህብረተሰቡ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል። ዘጋቢ ታዲዮስ ግርማ
የወባ በሽታን ለመከላከል በሚደረጉት ጥረቶች ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የበኩላቸውን ድረሻ መወጣት እንዳሉባቸው የየኪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አስታወቀ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች