በተለይም በሽታው ለመከላከል የትንኝ መራቢያ ቦታዎችን ማፋሰስና ማዳፈን ስራ ላይ ህብረተሰቡ ትኩረት አደርገው እንድሰራ ጽ/ቤቱ አሳስቧል።የኪ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተካልኝ ባሳ እንደገለጹት ለህብረተሰቡ ዋነኛ የጤና ስጋት የሆነውን የወባ በሽታን ለመከላከል የአካባቢ ንጽህና በመጠበቅ ዙሪያ ሰፊ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።እንደ ወረዳ ከ22ቱ ቀበሌዎች 14 የወባ መቀነት ተብሎ በተለዩት አካባቢዎች ግብረ -ኃይ ተቋቁመው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።ወቅቱ ቡና የሚሰበሰብበት በመሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ ከአካባቢው ርቀው ስለሚቆዩ በተለይ ሴቶችና ህጻናት ለበሽታው ስለሚጋለጡ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ኃላፊ ተናግረዋል። የአጎበር አጠቃቀምን በትክክል ተግባራዊ ማድረግ ከህብረተሰቡ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል። ዘጋቢ ታዲዮስ ግርማ
የወባ በሽታን ለመከላከል በሚደረጉት ጥረቶች ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የበኩላቸውን ድረሻ መወጣት እንዳሉባቸው የየኪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አስታወቀ።

More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ