የማህበሩን ይፋዊ ዓርማ ኮሚቴው አሳውቋል #ትርጓሜዎችን በሚመለከት#የተያያዙ እጆች ወንድማማችነትን ፣ ትብብርንና በጋራ ማደግን ፣#መሃል ክብ ውስጥ ያለው ቡና ችግኝ ልማትን/እድገትን፣እንዲሁም ካፋ የቡና መገኛ መሆኑን በተጨማሪም ጎንጋዎች በሚገኙበት አካባቢዎች ቡና በስፋት የሚመረት መሆኑን-#አረንጓዴው የተፈጥሮ ልምላሜን#ላይኛውና በታችኛው ፅሁፍ መሀል ያለው ነጫጭ ቀለበቶች ትብብርን፣መጀጋገፍን#ቢጫ ነጠብጣብ የወንድማማችነት መጠባበቅን ያመለክታል፣ለዓመታት ሳይገናኙ ተራርቀው የቆዩት የጎንጋ ህዝቦች ተገናኝተዉ በአንድነት ይመክራሉ።የእርስ በርስ ግንኙነትና ትብብርን በማጠናከር ነገን የተሻለ ለማድረግ ይመካከራሉ።ሁላችሁም የጎንጋ ህዝቦች እና ወዳጆች በዚህ ታሪካዊው የፎረም ቀን እንዲትገኙ አዘጋጅ ኮሚቴው ይጋብዛቸዋል ።
የጎንጋ ህዝቦች ልማትና ትብብር ፎረም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቴፒ ከተማ በመስከረም 25 እና 26/2017 ዓም ይካሄዳል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።