ድጋፉን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፋት የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ይህ ዓይነቱ ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረዉ ይሰራል ብለዋል።በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦችንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር 350 ለሚሆኑ ለተቸገሩ ወገኖች አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለእያንዳዳቸዉ የ 2 ሊትር ዘይትና የ4 ኪሎ ግራም ዱቄት ድጋፍ መበርከቱን የተናገሩት ደግሞ በቴፒ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ሊግ ሀላፊ ወይዘሮ ይጋርዱ ጤናዉ ናቸዉ። በተመሳሳይ በከተማዉ መዋቅር ዉስጥ የሚሰሩና ከ2 ሺህ ብር በታች የሚከፈላቸዉ 126 ደመወዝተኞችም ለእያንዳንዳቸዉ የ5 ሊትር ዘይት ድጋፍ ተሰጥቷቸዋል። ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ።
አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ 350 ለሚሆኑ በቴፒ ከተማ ለሚኖሩ አቅመ ደካማ ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ መበርከቱ ተገለጸ።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።