የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኬኒያ ናይሮቢ የሚገኘው የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሠራተኞች በስራ ማቆም አድማ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ወደ ናይሮቢ የሚያደርገው በረራ በታቀደለት መርኃ ግብር እየተከናወነ አለመሆኑን አስታውቋል። አየር መንገዱ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ እንደሚገኝ በመግለፅ በክስተቱ ለተፈጠረው መስተጓጎል ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል። ደንበኞች የበለጠ መረጃ ለማግኘት የዓለም አቀፍ የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል ስልክ ቁጥር በ+251 11 617 9900 ወይም በ 6787 በመደወል አልያም ናይሮቢ የሚገኘውን ትኬት ሽያጭ ቢሮ በአካል በመገኘት ማግኘት እንደሚቻል አየር መንገዱ አስታውቋል።
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ