ችግሩ መፍትሔ ለማበጀት ከሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ጋር እየተሰራ መሆኑንም ወረዳው አሳውቋል። በሸካ ዞን ማሻ የምርጫ ጣቢያ ተመራጭ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አዝመራ አንደሞና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ጉብኝት ተደርጓል። የሬድዮ ጣቢያችን የሸካ ዞን ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ካዳኔ ከሲቶ በስልክ በስልክ በሰጡት መረጃ አራት ብሎክ ያለው የጤና ጣቢያዉ በ2008 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን ስራው ያስጀመረው ኮንትራክተር ስራ በማቋረጡ ምክንያት ተጓቶ መቆየቱን አንስተው አሁን ላይ ከአድስ ኮንትራክተር ጋር በመሆን የተለያዩ ማሻሻያዎችን በማድረግ ግንባታው ወደ መጠናቀቁ ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል።
ዘጋቢ ሀና ግርማ
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ