ችግሩ መፍትሔ ለማበጀት ከሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ጋር እየተሰራ መሆኑንም ወረዳው አሳውቋል። በሸካ ዞን ማሻ የምርጫ ጣቢያ ተመራጭ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አዝመራ አንደሞና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ጉብኝት ተደርጓል። የሬድዮ ጣቢያችን የሸካ ዞን ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ካዳኔ ከሲቶ በስልክ በስልክ በሰጡት መረጃ አራት ብሎክ ያለው የጤና ጣቢያዉ በ2008 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን ስራው ያስጀመረው ኮንትራክተር ስራ በማቋረጡ ምክንያት ተጓቶ መቆየቱን አንስተው አሁን ላይ ከአድስ ኮንትራክተር ጋር በመሆን የተለያዩ ማሻሻያዎችን በማድረግ ግንባታው ወደ መጠናቀቁ ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል።
ዘጋቢ ሀና ግርማ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።